Tuesday, April 24, 2012

ነገር የገባት ቆቅ


መጓዝ ለኔ ማወቅ ነው….በሄድንበት ወይም በተጓዝንበት ቦታ ሁሉ አዲስ ነገር ይገኘኛል አዲስ አየር፤አዲስ ሰው ፤አዲስ አስተሳሰብ ፤ወግ ባህል፤አዲስ ፍቅር አዲስ አዲስ አዲስ ነገር…….፡፡ መጓዝ ለኔ እንዲህ ነው፡፡ አንድ ስሙን የማላስታውሰው የሀገሬ ሰው #ሀበሻ የቆመበት ቦታ መቀበር ይችልበታል ; ይላል፡፡ እኔም እስማማለሁ…..በዚህች በትንሽ የህይወት ዘመኔ በርካታ ወዳጆች አፍርቻለሁ፡፡ ከምሁር እስከ ነጋዴ አቅም ያላቸው ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች…..መብታቸው እንደጠጠበቀ ሆኖ ታሪክ ከማወቅ ተፈጠሮን ሀገርን ከማወቅ በዘለለ አንድ መጠጥ ግሮሰሪ ውስጥ ወይም ኮማሪት ቤት በርካታ አጫፋሪ በመሰብሰብ ወይም ወግ ደላቂ በማዋቀር ብርጭቆና ጠርሙስ እያጋቡ በሚረጩት ብር ጀግንነታቸው እንዲነገርላቸው እንዲወደሱ የሚፈልጉ ድንገት ስለታሪክ ስለሃገር ሲነሳ የሚያማቸው ወይም ሲጠየቁ ግራ የሚገባቸው ብዙ ወዳጆች አጋጥመውኛል፡፡ልድገመው (መብታቸው ግን እንደተጠበቀ ይቆይ) ነገር ግን ከዚህ መሃል ላይ መገኘት ግን ምን ያህል አለመታደል እንደሚሆን ገምቱልኝ……ጋዜጠኛና ደራሲ ነብይ መኮንን ( አዲስ አድማስ ) ጋዜጣ ሳገላብጥ እንዲህም የሚል አስነበበኝ፡፡
ኤልዳስ ሄክስ ሌይ የተባለ ታዋቂ ደራሲ እንዲህ ሲል መስክሯል (መጓዝ ማንም ሰው ስለሌሎች ሀገሮች መሳሳቱን ለማወቅ ይጠቅመዋል) ይለናል ፡፡ አቦ እኔም እስማማለሁ…… እንዲህ እንደማለት እኮ ነው….የሆነች ልጅ አይተሃት መስሪያ ቤት ወይም የሆነ ቦታ ሊሆን ይችላል ወይም በምተለብሰው አጭር ጉርድ ቀሚሷ ወይም ከንፈሯን በምትቀባው ቀይ ሊፒስቲክ ሰበብ ወይም ፍጥን ፍጥን በሚለው አነጋገርዋ የሆነ ስም ፈጥረህላት ቆይተሀል አንተ ጠልተሀት ሌላውንም አሳድመህ ሰንብተሀል…..ግን በአጋጣሚ ቀርበሀት፤ተግባብተሀት ያ…ሁሉ ግምትህና ልፋትህ መናሲቅብህ እንደማለት ነው፡፡እናም የነበረን ግምትና በአይን አይቶ የማረጋገጥ መሀል ያለውን ሰፊ ክፍተት ያስረዳናል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ነብይ መኮንን ሳላደንቅ ሳላመሰግን ባልፍ ይቆጨኛል፡፡ በሄደበት ፡በተቀመጠበት ሁሉ ያየውን፤የሰማውን፤ያሸተተውን፤የቀመሰውን ጽፎ ያስነብበናል…ያወቀውን ያሳውቀናል……ጣትህ ይባረክ በየዋለሁ እኛም እንከተላለን፡፡ አሜን! ፡፡
ሀገሬን ጠቅልዪ የማየት ህልም አለኝ፡፡ ( ይሄ የሁላችሁም ምኞት እንደሚሆን አልጠራጠርም ) እንደ አጋጣሚ ሆኖ በርካታ ቦታዎችን ጎብኝቻለሁ፡፡ እሳት ከሚዘንብበት ከሚመስለው እትዩ-ጅቡቲ ጠረፍ ጋላፊ አንስቶ በአራቱም አቅጣጫ እዛም አዚም በትንሽ በትንሹ፡፡ መቼም ለኔ ነፍሴ ሀሴት የደስታ ጣራ ላይ የምትደርሰው ወደ ደቡብ ስጓዝ ነው……በቃ ልቤ ጮቤ ይረግጣል፡፡ ወድጄም አይለም ሀሳብና ጭንቄን በትክክል ሳጥን ውስጥ የሚቆለፉት ያኔ ነው ተመላልሼ ደጋግሜ አይቼዋለሁ የደቡብን መንገድ ስጀምር ሰላም አገኛለሁ…..ተፈጥሮን ለመቋደስ ፤ ለማጣጣም ብሎም ለኪነጥበብ ውስጥ ለመመላለስ በተመስጦ ለማሰብ ያመቻል ወይም ያመቸኛል……….ቆይ አንድ አጋጣሚ ላስታውሳችሁ፡፤ ታዋቂው ዘፋኝ ቴዎድሮስ ካሳሁን በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንዲህ ሲል የሰማሁት መስሎኛል፡፡(ጃ ያስተሰርያል ) የሚል ሀገር ያናወጠ ሃሪፍ ስራ ሰርቶ ነበር እናም እሱ ልብ ውስጥ ገብቼ ስሜቱን ባልናገርም ስራወን እንደ ጨረሰ ለሊቱን ሙሉ ወደ ሀዋሳ ሲነዳው እንዳደረና ደስታውንም ከሀዋሳና ከሃዋሳ ህዝብ ጋር እንዳሳለፈ ተናግሯል፡፡እኔም ልመስክር አጋጣሚ ሆኖ እዛ በነበርኩበት ወቅት ቴዲን አይቼዋለሁ እናም እነዛን ቱባ ስራዎች የሚፈጥረው አዋሳ ሀይቅ ዳር ሆኖ ይሆን እንዴ ? ብዪ ጠረጠርኩ፡፡

አሁን ሀዋሳ ደርሻለሁ፡፡ እዚህ ፍቅር አለ አሞራ ገደል ከዋርካው ጥላ ስር ትኩስ ፍቅረኛሞች ተካቅፈው ፍቅር ሲጎራረሱ ታያለህ ወፎች ይዘምራሉ የተለያየ ድምጽ ነው የሚያወጡት የሆነ ደስ የሚል ሽታ ደሞ አለ የአበባ፤የግራር ወዘተ…..ሀይቁ ላይ አሶች ሲደንሱ ፤አባ ኮዳ፤ጦጣ ፤ጉሬዛ እየተቀባበሉ ትርኢት ሲያሳዩ ትደመማለህ ታቦር ተራራ ከሩቁ ና ወዲህ ይልሃል ሀዋሳን ሊያስጎበኝህ የሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ታሪካዊ  ቪላ ቤትም እዛ ይገኛል ከዛ በላይ ደግሞ በዙ አርቲስቶች የሚጎበኙት የሚታደሙበት አንድ ቤት አለ ሙዚቀኛው፤ደራሲው፤ሰዓሊው፤የትያትር ባለሙያው ቤቷን ሳይሳለም አይመለስም፡፡ ምናልባት ባለቤቶቹ ለኪነ ጥበብ ቅርብ ስለሆኑ ብዩ ገምቻለሁ፡፡ መስተንግዶአቸው ልዩ ነው…እኔም ማረፊያዩ እዛው ነው፡፡ በርካታ አርቲስቶች ተሰብስበው አጋጠሙኝ ቀደም ብሎ የግቢው መናፈሻ ውስጥ የታየኝ ገለታ ነው አርቲስት ገለታ ተ/ጻዲቅ ደስ ከሚለው ጢሙ ጋር….በረንዳው ላይ አርቲስት ችሮታው ከልካይ፤ፋንቱ ማንዶዩ፤ጋጋ፤ፍልፍሉ ሌሎች በርካታ አርቲስቶች ይታዩኛል ተራ በተራ ተዋወኳቸው ደስታዩ ወደር አልነበረውም እንዴት ደስ ይላል ! ፎቶግራፍ ማንሳት ጀመርኩ……ድንገት ፋንቱ ማንዶዩ ጠራኝ
# ስማኝ ወንድም ላስቸግርህ ; አለኝ
# ãረ ችግር የለም ምን ልታዘዝ ; አልኩት
#ይኀውልህ እኔ ህጻን ልጅ ቶሎ አይቀርበኝም ፊቴ ያስፈራቸዋል፤ድምጼ ያስበረግጋቸዋል ይህችን ልጅ ግን ተመልከታት ገና ስጠራት ሮጣ መጣች አውቅሃለው አለቺን የምጠይቃትን ሁሉ በንቃት ትመልሳለች ልቧ የአርቲስት ነው ( ነገር የገባት ቆቅ ነች ) ; ፡፡ አለና ወደራሱ አስጠጋት
# በል ፎቶ አንሳኝ በጣም ነው የሚያስፈልገኝ ደግሞ መርቄያታለሁ አርቲሰት ሁኚ ብዩ ;
አለና ለፎቶ ተዘጋጀ እኔም አነሳሁት ደጋገምኩት ከዛን ጊዜ በኋላ ፋንቱ ማንዶዩን በአካል አግኝቼው አላውቅም አርቲስት ችሮታው ከልካይን ግን ትግራይ መቀሌ አገኘሁት አላመነም የመሃል ሀገር ሰው ሰሜን ጥግ ያውም ባልተገመተ ሁኔታ….፡፡ ቆንጆ ጊዜ አሳለፍን አንድ ዝግጅታቸውን ጋበዘኝ ማስታወሻ ፎቶ ተነስተን ተለያየን::
ይህች ነገር የገባት ቆቅ እድሜ ጨምራለች፤ጨዋታም እንዲሁ ፋንቱ ማንዶዩ ምን እንደቀባት አላውቅም ልጅቷ የምታሳየው ጥበብ የተለየ ነው የከርሞ ሰው ይበለንና እንጽፈዋለን !!::    


No comments:

Post a Comment