Wednesday, April 25, 2012

የሃይሌ ጽናት



ጀግናውን እንዴት እንዳገኘሁት !
       በወረሀ ሰኔ እሁድ ማለዳ 4ሰዓት ገደማ አዲስ አበባ ስቴድየም አካባቢ ዙርያ በዝግታ እየተራመድኩ ነው……..! ምክንያት ፡- በስቴድየም ዙርያ አንዳንድ የተዘጉ በሮች ጥግ ጥላ ተከልለው መጽሀፍ የሚሸጡ መጽሀፍ ነጋዴዎችን ለመጎንኘት ነው፡፡ ድንገት በጥላ ፎቅ መቀመጫ በስተግራ በኩል ያለው የተመልካች መግቢያ በር ክፍት ሆኖ አየሁ ፡፡ ምን ሊኖር ይችላል ብዩ ዘው ብዩ ገባሁ…….ማንም የጠየቀኝ የለም የኳስ ሜዳ ሳሩ ላይ….ግማሾች በመሮጫው ሜዳው ላይ በህብረት በህብረት ሆነው ሴቶች ለብቻ ወንዶች ለብቻ እሩጫ የሚሰለጥኑ አትሌቶች ተመለከትኩ…፡፡ሁሉም አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለው ቱታ ለብሰው ደምቀዋል……! ፡፤ እንዴት ደስ ይላል፡፡ እነማን እነንደሆኑ ለመለየት ያዳግታል፡፡ ድንገት እንደኔው አጥር ተደግፎ የታደመውን ልጅ እግር  ጠየኩት፡፡
# ወንድም የማን ቡድን ሯጮች ናቸው ? ; አልኩት እጁን ነካ አድርጌ
# ብሄራዊ ቡድን ናቸዋ ! አታውቃቸውም እንዴ ? ; መልሶ ጠየቀኝ …… ባውቅማ ለምን እጠይቀዋለሁ ? መልሼ ጠየኩት፡፡
# በናትህ ዕረ አላወኩም ታድያ ብሄራዊ ቡድን ከሆነ እዚህ ውስጥ ሃይሌ ገ/ስላሴ ፤ደራርቱ ቱሉ ይኖሩ ይሆን? ;አልኩት በጉጉት ልቤ በደስታ ልትቆም ደርሳለች
# አዎ አሉ…! እንደውም ያውልህ ከፊት ከሚሮጠው አትሌት ጀርባ የሚከተለው እሱ ነው እ እ እ……. ያቻትልህ ደራርቱ ግንባሯ ላይ ነጭ ጨርቅ ያሰረችው አሁን እንደውም ሳሩ ላይ ቁጭ ያለችው ; አለኝ፡፡ አይኔን ማመን ነው ያቃተው…..! ዓለምን ጉድ ያሰኘ ስመጥር ጀግና አትሌት በቅርብ ርቀት በዓይኔ በብረቱ እያየሁት ነው…..! ደስታ ፤ ፍርሃት…. የሆነ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ተሰማኝ ! ፡፡ በቴሌቪዥን መስኮት ሃገሩን ወክሎ አለም አቀፍ ሩጫ ሲሮጥ ልቤ አብሮት ሮጧል…….ተፎካካሪን ጥሎ ሲገባ ! ፤በደስታ ባንዲራ ለብሶ ሲጨፍር ! በደስታ አልቅሻለሁ፡፡ የኔ የወንዜ የሃሀሬ ልጅ በመሆኑ ኮርቻለሁ ፡፡ ዓለም ዝቅ ዝቅ ያደረጋትን ፤የናቃትን የሀገሬን ባንዲራ ከፍ ብሎ እንዲሰቀል ፤ እንዲውለበለብ አድርጓል ……ሀይሌ ለሃገሩ ደምቷል….! ቆስሏል …….! ከዚህ በላይ ማለት አልችልም የተባለ ለመድገም ካልሆነ  በስተቀር….፡፡
    # ሄጄ ማነጋገር አለብኝ….. ግን ደግሞ ምን ብዩ ? እንዴትስ ሆኖ ? ማንስ ያስጠጋኛል ?;
ራሴን ጠየኩ…. መልስ የለም…… አይኔ ጀግናው ላይ ተተክሎ ቀርቷል ስቴድየሙን እየዞሩ ነው አሁንም ሀይሌ ከኋላ ነው የሚከተለው …..የሴቶቹ ቡድን ሩጫቸውን ጨርሰው ደራርቱ ከተቀመጠችበት ቦታ ላይ ተሰብስበው ተቀመጡ ሁሉም ፊት ላይ በድካም ውስጥ ፈገግታ ይነበባል ይሳሳቃሉ አንዷ ከአንዷ ትከሻ ላይ ተደጋግፈው፤አንገት ለአንገት ተቃቅፈው  ሳይ አንድነታቸው ፍቅራቸው አስቀናኝ…….! የወንዶቹ ቡድን የሩጫ ስልጠናው አላለቀም ፡፡ አሰልጣኝ ዶ/ር ወልደመስቀል ኮስትሬ ደረታቸው ላይ ያንጠለጠሉትን ትልቅ ሰዓት እየተቆጣጠሩ ፍጥነት እንዲጨምሩ በእጃቸው ምልክት ይሰጣሉ…….አሁን ሀይሌ ፍጥነት ጨመረ እንደ ሰጎን እየተምዘገዘገ እንደ አንበሳ እያገሳ፤እንደ አቦ ሸማኔ እየተለመጠ  ሌሎችን እየሳበ ይሮጣል……..ድንገት በሚስማር ተራ መታጠፊያ መአዘን ላይ ሲደርስ ግን እግሩን ማነከስ ጀመረ ብዙም አልቆየ ከሯጮቹ ተነጥሎ በዝግታ እየተራመደ ሜዳ ላይ ከነበረው ነጭ ፕላስቲክ ወንበር ላይ ተቀመጠ ……፡፡ አሁን ነው ሰዓቱ አልኩኝ በሆዴ ሄጄ ማነጋገር አለብኝ በቃ ወድሃለሁ ! ፤አከብርሃለሁ ! ፤አንተ የኛ ጌጥ ነህ ! ፤ ጀግና ነህ ! ልለው ይገባል አልኩ በስሜት…….፡፡
                            ©   ©   ©
          ስቴድየም ውስጥ ዙረያውን ወንፊት በሚመስል የሽቦ አጥር ታጥሯል ወደ ውስጥ ዘልቆ መግባት አይቻልም …ጨነቀኝ ፡፡ ዘዴውን ያውቅ እንደሆነ ከጎኔ ያለውን ልጅ አሁንም አስቸገርኩት፡፡
# ወንድም ወደ ውስጥ እንዴት ነው ሚገባው ? ሃይሌን ማግኘት ማነጋገር እፈልጋለሁ …..! ; አልኩት አይን አይኑን እያየሁ፡፤
# መግባት ትፈልጋለህ ? እንግዲህ ከቀናህ ይኅውልህ ፖሊሱ የቆመበት ቦታ ወደ ውስጥ የሚያስገባ በር ነው ጠባቂውን ለምነው….. ከፈቀደልህ ትገባለህ በል ይቅናህ ; አለኝ፡፡ በስተቀኝ በኩል ያለውን የመግቢያ በር እየጠቆመኝ ፡፡ ስለትብብሩ አመሰገንኩት… የጠቆመኝ መግቢያ ግን ፈጽሞ በር አይመስልም ተመመሳሳይ የሽቦ አጥር ነው ፡፡ እየተጠጋሁ በመጣሁ ቁጥር ግን ክፍቱን ያለ ያልተቆለፈ በር አየሁ…ፖሊሱ አሁንም እዛው ነው፡፡ ልለምነው አለምነው ከራሴ ሙግት ገጥሜ ደቂቃዎች አለፉ፡፡ ድንገት ከአጥሩ ውጪ ሙሉ ቱታ የለበሰ ሰው የአጥሩን በር ከፍቶ ሲገባ ተከትየው ገባሁ…ፖሊሱ አልጠየቀኝም ከሰውየው ጋር ይሆናል ብሎ እንዳሰበ ገመትኩ ሀይሌ አሁንም ወንበሩ ላይ ተቀምጧል በጣም እየቀረብኩት ነው ፡፡ ወጌሻው ቀኝ እግሩ ታፋ ላይ ፋሻ ጠቅልሎለት ስራውን ጨርሶ ሄዷል…….፡፡ አሁን እኔና ጀግናው ሀይሌ የአንድ እርምጃ ልዩነት ነው ያለን አላየኝም ፊቱ በላብ ተጠምቋል ግንባሩ ላይ በትንሽ በትንሹ የተቋጠሩ የላብ እንክብሎች ይታዩኛል ፡፡ ጀግንነቱን አይበገሬነቱን አይቶ ብቻ መመስከር ይቻላል ልቤ ከኔ ጋር መኖር አለመኖርዋን ለማረጋገጥ እጄን ወደ ደረቴ አስጠጋሁ…..!
 #ጤና ይስጥልኝ ሃይሌ……; አልኩት ያለኝን ሀይል ፤ ጉልበት ሁሉ አጠራቅሜ ቀና ብሎ አየኝ ፡፡ በድካሙ ውስጥ ፈገግታው አለ………………
# ጤና ይስጥልኝ ደህና ነኝ ; አለና እጁን ዘርግቶ ጨበጠኝ ፡፡ እጁ በጣም ይለሰልሳል ጥንካሬው ግን እንዳለ ነው ማመን አቃተኝ በህልም የሆነ ያህል ነው የተሰማኝ ፡፡
# በጣም አድናቂህ ነኝ ሃይሌ ዛሬ አንተን በማግኘቴ ትልቅ እድለኛ እንደሆንኩ ነው የምቆጥረው ; አልኩት፡፡
# እሺ በጣም ነው የማመሰግነው ፡፡ የአዲስአበባ ልጅ ነህ ? ; አለኝ፡፡
# አይ አይደለሁም የክፍለ ሃገር ልጅ ነኝ ;
# ታስታውቃለህ ጥርስህ ይናገራል ! ; አለኝ ፍሎራይድ ያበላሸውን ጥርሴን መቅላት እየተመለከተ ፡፡ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚኖር ሰው ከውሃው ከሚመጣ በሙሉ የዚህ ችግር ተጋላጭ ነው፡፡
# የናዝሬት ልጅ ነህ ? ;
# እዛው አካባቢ ነኝ ብዙም አልርቅም ; አልኩት…….፡፡ ጊዜ ሰጥቶ እያወራኝ መሆኑ ደስ ብሎኛል ከዚህ በላይ ምን እጠይቀዋለሁ…. ጀግናው አንገቱን አቀርቅሮ የግራ ታፋው ላይ የተጠቀለለውን እግሩን እያሻሸ ፤ እየነካካ ነው የህመም ስሜት እየተሰማው መሆኑ ፊቱ ላይ ያስታውቃል
#ሀይሌ ምን አጋጥሞህ ነው ?; አልኩት፡፡
# ትንሽ የጡንቻ መሸማቀቅ ነው ለክፉ አይሰጥም ከባድ ልምምድ ስላደረኩበት ነው ይተወኛል ; አለኝ ፡፡ ፈጣሪን ለመንኩለት እንዲሻለው ፡፡
በቃ #እወድሃለሁ; አልኩትና ብዕርና ወረቀት አስጠጋሁለት
# እዚች ጋር ፈርምልኝ ; አልኩት፡፡
# እሺ ምን ችግር አለ ; አለና ስሙን ጽፎ ፈረመልኝ፡፡ ከዚ በላይ መቆየት አልቻልኩም የወንድ ሯጮቹ ቡድንም ሩጫውን ጨርሰው ሀይሌ ወደተቀመጠበት ቦታ እየመጡ ነው፡፡ ለስንብት እጄን ዘረጋሁለት በምላሹ በፍቅር ጨበጠኝ…….! የዚህን ጀግና ፍቅር ! ፤ ስሜት አይበገሬነት ! ፤ ስምና ፊርማውን የያዘ ወረቀት ይ¹ ወደ ቤቴ ገሰገስኩ፡፡ በጥንቃቄ ፎቶ አልበሜ ውስጥ ፊርማውን ማህተብ አኖርኩ……፡፡ ይኅው እስከዛሬ በማስታወሻ የያዝኩት ፊርማ አብሮኝ አለ ፡፡ የዛኑ ቀን አመሻሽ ላይ ለሱ ያለኝን ፍቅርና አድናቆት በግጥም ጽፌ አስቀመጥኩ፡፡
                          ©    ©    ©
       ጀግናው ሻለቃ ኀይሌ ገ/ስላሴን ከዛን ጊዜ ወዲህ በአካል አይቼው ፤ አግኝቼው አላውቅም…የጻፍኩትን ግጥም ማስታወሻ ትሆነው ዘንድ ልሰጠው አስቀምጨ ድፍን አስራ ሶስት ዓመት አስቆረ……. ፡፡ እነሆ ዛሬ ከቆለፉኩበት ሳጥን ውስጥ አውጥቼ አየር ላይ እንድለቀው ያደረገኝ ምክንያት በቅርቡ በኤሌክትሮኒክስ መረጃ መረብ አንድ አስተያየት ሰጪ ስለሃይሌ ከሰይፉ ፋንታሁን (ጋዜጠኛ) ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስና ቃለ ምልልሱን ተከትሎ፤-   ኃይሌ የወርቃማው እግሮችህ ውለታ በምላስህ እንዳይደበዝዙ ! በሚል ርዕስ ስር የተሰጠ አስተያየት (የአስተያየት ሰጪውን መብት ባከብርም) እኔ ግን ያልተዋጠልኝና በተለይ ከትልልቅ ሰዎች ጋር የሚደረግ ቃለ ምልልስ ጠያቂው ወይም ጋዜጠኛው ስለ ተጠያቂው ስለ ሚጠይቀው ጉዳይ በቂ እውቀት እንዳለው የማወቅ ሃላፊነት ያለበት ይመስለኛል…… የሚጠየቀውም ተጠያቂ ከሚጠየቀው ርዕስ ጋር ተዛማጅነት እውቀት መኖሩን ሳያረጋግጥ በሚሰጥ መልስ የሚያስከትለው መዘዝ በተለይ በታዋቂ ሰዎች የከፋ ነው ፡፡ ዞሮ ዞሮ በዚህ ጉዳይ ወደፊት እመለስበታለሁ::
   ሃይሌ ግን ዛሬም እግሩም ልቡም ለሀገሩ እንደሚሮጥ ግን ተስፋ አደርጋለሁ……
እውን ሀይሌ ሀይህችን ግጥም ትደርሰው፤ያነበው  ይሆን ??!! ፡፡


No comments:

Post a Comment