Tuesday, April 24, 2012

ጠረኔን መልሱ

ይህችን ግጥም ስጽፋት ወደ ደቡብ አርባ ምንጭ ለመዝናናት ሄጄ ነው፡፡ ወዳጆቼ ከአድማስ ማዶ ከተሰደዱበት ሃገር ሲመለሱ መጀመርያ የሚያገኙት እኔን ነው፡፡
# አቦ ወጣ እንበል ; እላቸዋለሁ
# እሺ አንተ እንዳልክ ; ይሉኛል… ፕሮግራሙን እናቅዳለን ፡፡ ረዘም ያለ ጉዞ ይመቸኛል ! ተፈጥሮን እየኮመኮሙ ንጹህ አየር እየሳቡ ፤ እየቀዘፉ መጓዝ መጓዝ………! ፡፡
ቀኑ የገበያ ቀን ነው አርባ ምንጭ ላይ…… ከዋናው የከተማዋ አደባባይ በስተ ገራ አንድ ፎቅ ያላት ቆንጆ ኬክ ቤት አለች ማለዳ ላይ ተሰብስበን ቡና እየጠጣን ነው የሃመር ኮረዶች በአጠገባችን እያለፉ አየሁ
# እንዴ ከየት ነው የመጡት ?; አለ አንዱ ዲያስፖራ ጓደኛችን……. እውነቱን ነው ወደ ሃመር ቱርሚ ለመሄድ ቀጠሮ ይዘናል ! እነሆ እነሱ ቀደሙንና አየናቸው…………፡፡
ገበያ ሲሆን አንድ አንድ ጊዜ ብቅ እንደሚሉ ተነገረን በከተሜው ሰው……!
ድንገት አንዷ የሃመር ወጣት ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ……….! ልብ የሚሰልብ ውበት አላት……! ፡፡ እናም ብእሬን ከወረቀት አዋደድኩ፡፡
© © ©
ማስታወሻነቷ ለነ እንትና ነው፡፡ ልድገመው ለነ ( እ….ን…..ት….ና ! )

1 comment:

  1. Art 4 art sake or Art 4 social sake, where r u? Really i like Ur observation and the potential 2 be critical observant.

    ReplyDelete