Monday, April 30, 2012

በዓሉ ግርማ


                        በዓሉ ግርማ
                                                                                 (1928 - 1976/)

                 ደራሲ በዓሉ ግርማ በኢላባቡር ክፍለ ሀገር ሱዼ በሚባል ሥፍራ 1928/ ተወለዱ::
ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርሥ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በልዕልት ዘነበወርቅ /ቤት: ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በጄኔራል ዊንጌት /ቤት አጠናቀዋል:: ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖሊቲካል ሳይንስ እና ኢንተርናሽናል ሪሌሽንስ የቢ.. ዲግሪ ያገኙ ሲሆን: በዚሁ ተመሳሳይ መስክ ከአውሮፓ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል::
ከጻፏቸው በርካታ ድርሰቶቻቸ ውስጥ "ከአድማስ ባሻገር" የተሰኘው መጽሐፋቸው በሩሲያ ዊያ ተተርጉሞ በቀድሞዋ የሶቪየት ሶሺያሊስት ሕብረት ሪፑብሊክ ቀርቧል::
በጋዜጠኝነት
የዛሬይቱ ኢትዮጵያ የመነን መጽሔት የአዲስ ሪፖርተር መጽሔትና;የአዲስ ዘመን ጋዜጣ  ዋና  አዘጋጅና: በኢትዮጵያ ራዲዮም አገልግለዋል::
የመጨረሻው መጽሐፋቸው "ኦሮማይ" በወቅቱ በነበረው የደርግ መንግስት ሊደገፍ ባለመቻሉ: 1976/ ለደራሲው ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሊሆን በቅቷል::

ድርሰቶቹ
*
ከአድማስ ባሻገር
*
የኅሊና ደወል
*
የቀይ ኮከብ ጥሪ
*
ሐዲስ
*
ደራሲው
*
ኦሮማይ
        የዚህን ድንቅ ጸሀፊ ልብ ወለዶች ከሞላ ጎደል አንብቤያቸዋለሁ ደራሲ በአሉ ግርማ ልብ የሚመስጥ ልብ ወለድ ጽፎልናል፡፡ እኔ ብዙ ማለት አልችልም የተባለ ለመድገም ካልሆነ ! እጅግ በጣም የሚገርመኝ ግን ገጸ-ባህሪ አሳሳሉ ነው በተለይ ሴት ገጸ ባህሪን ሲስል ያቺ ሴት በእውኑ አለም ያለች ያህል እንዲሰማን የማድረግ ሃይል አለው ምሳሌ ብጠቅስ…………. የአድማስ ባሻገሯ ሉሊት ፤ኦሮማይ ላይ ያለቺውና የነገሰችው መቼም የማትረሳው ፊያሜታን ማንሳት እንችላለን በተለይ ፊያሜታ ጊላይ ምንጊዜም ከህሊናዩ የምትጠፋ አይደለቺም ! በተለይ በአሉ ግርማ በሷ ውስጥ የተናገረባት ፤ የልቡን የውስጡን የተነፈሰባት ደብዳቤዋን እጄ እስኪደማ በወረቀት ገልብጨዋለሁ…….. በተወሰነ ጊዜዎች እስከ ዛሬ ድረስ እያነሳሁ  አነበዋለሁ አይሰለቸኝም !  ምን ይሄ ብቻ ፊያሜታ ጊላይ የምተቀባው ቫኔል ፋይፍ ሽቶ ምን ጊዜም ከህሊና አይረሳም ! ያን ሽቶ አይቼው አሽትቼው ባለውቅም ጥሩ ሽቶ ባየሁ ባሸተትኩ ቁጥር ተመስጫለሁ፤አስቤዋለሁ፡፡ መጽሀፉ በወጣ ሰሞን የሃገሬ ቆነጃጅት ወጣት ሴት ሁሉ በተለይ በመዲናችን አዲስ አበባ ፊያሜታ ምትጠጣውን መሎቲ ቢራ በስፕራይት መጠጣት ፋሺን ሆኖ ፤ሀገሩን አጥለቅልቆት እንደነበር በወቅቱ የነበሩ ሰዎች አጫውተውኛል ፡፡ የዚህን ያህል ደራሲው ገጸ-ባህሪ መሳል ይችልበታል ! ሌሎች ብዙ ልትሉ ትችላላሁ ወይ ብትሉን ደስታዩ ወደር የለውም፡፡ እኔ ግን ፊያሜታን በደራሲው ልብ ውስጥ ሆኘ እያሰብኩ የገጠምኳትን ግጥም በቀጣይ ጊዜ እለጥፈዋለሁ፤ አስነብባችኋለሁ እስከዛው በደራሲው የመጨረሻ ቃል እንሰናበት፡፡
#............;
እንባ እንባ ይለኛል
ይተናነቀኛል………
እንባ ግን የታባቱ
ደርቋል ከረጢቱ
ሳቅ ሳቅም ይለኛል
ስቆ ላይስቅ ጥርሴ
ስቃ እየነደደች
መከረኛ ነፍሴ፡፡
  © © ©
  ኦሮማይ
   

Saturday, April 28, 2012

አይኔን ባይኔ


   ይህችን ግጥም በጣም መልእክት የምትሰጠኝ ግጥም ነች፡፡ ስንቶቻችን ነን መሆን ያለብን ሌላ እየሆንን ያለነው ሌላ አይነት ሕይወት የምንመራ?፡፡

Friday, April 27, 2012

ናፍቆቴን ነጠኩኝ


ናፍቆቴን ነጠኩኝ
    አንድ በኤለክትሮኒክስ መረጃ መረብ የተዋወኩት ወዳጄ እንደዋዛ በስራ አጋጣሚ በአንድ በኩል እንጀራ§ን እየጋገርኩ በአንድ በኩል የመጻፍ ማወቅ ስሜቴን እየተወጣሁ ሳለ ተዋወቅን ፡፡  ገጣሚ ነው ደስ ደስ የሚል ግጥሞች ይጽፋል….. እናም እኔ እንደቀልድ የምለጥፋቸውን ግጥሞች በጣም ይወዳቸዋል ሳይታክት አስተያየት ይሰጠኛል………..! በጣም ሳላመሰግነው አላልፍም ምክንያቱስ ብትሉ ስንት ዓመት ከወረቀት ከማንበብ ተለይቼ እኮ ነው ደንገት መነቃቃት የጀመርኩት ……..ሀሪፍ አይደል !!!! አንድ ግን አክሎ አስተያየት ሠጠኝ ፡፡ ምን አለ መሰላቹ…..
# ወዳጄ አደም ግጥሞችህን በጣም ወዳቸዋለሁ ተመቹኝ ግን ማብራሪያ ታበዛለህ ; አለኝ ፡፡
   ልክ ነው ከምለጥፋቸው ግጥሞች ጋር የተለያዩ ታሪኮች አሉ ግን የግጥሙ ማብራሪያዎች አይደሉም እራሳቸውን የቻሉ (የጉዞ ማስታወሻ ፤ወግ፤ገጠመኝ፤ወዘተ…… ) ሊሆን ይችላል ወይም ናቸው፡፡ ከሙሉ ትረካ ቦጨቅ እያደረኩ ነው የምለጥፈው እንጂ ሙሉ ሙሉ ታሪኮች ናቸው ፡፡ የጻፍኩትን ሁሉ ቢሆንማ  አታነበውም ብዙ ነዋ ! እሳት ላይ ሆኖ እንዴት ይነበባል ???? መስመር ላይ ደግሞ ሰዎች ይጠብቁሃል ምናልባት በፌስ ቡክ የለጠፈችውን ፎቶ አይተህ የጠስካት ወይም የተዋወካት ልጅ ልታወራህ ትፈልጋለች ስለምትወደው ፒሳ፤ ስለምትጠላው  ነገር ወይም ሻኪራ ስለለበሰቺው ልብስ እያወራችህ ነው….. መቼም ቀይ ሲበራ ደብዳቤ (message) ሲደርሰው ማን ደስ የማይለው አለ ? ሌላው ደግሞ በእርግጥ የእውነት ብዙ ጊዜ ስትፈልጋት የኖረች የድሮ የሰፈር ልጅ አግኝተህ ናፍቆትህን እየተወጣህ ሊሆን ይችላል ፎቶግራፏን ስታይ በጣም ወፍራብህ፤ወይም አምሮባት ወይም ባል አግብታ ከልጆችዋ ጋር አንዴ ዛፍ ስር አንዴ ሶፋ ላይ ቁጭ ብላ የተነሳችውን ምስሏን እያደነቅህ ይሆናል….. ስለ ተለዋወጥካቸው ፖስት ካርዶች፤ስለ ድሮ ትምህርት ቤት፤ስለፍቅር ደብዳቤ……. ሰፈር ውስጥ በአንዲት ሴት ልጅ ስለተጣሉት ጎረምሶች እያወራህ ነው……. ስለዚህ የተቦጨቀ ታርኮች መለጠፍ የግድ ሆነ……
                  "   "   "
መቼ ለት ነው….; ቅዳሜን ወዳታለሁ ብያችሁ ነበር አይደል …..! አዎ በጣም ነው የምወዳት ከምወዳቸው ወዳጆቼ ጋር የምታገናኘኝ ቀን ነች ሁላቸውም የተለያየ ስራ፤ ፍላጎት ፤ዝንባሌና ባህሪ የተላበሱ ናቸው በተለይ ከቀጥር በኋላ ደስ ሚል ጊዜ እናሳልፋለን እዛም እዚም ላፕ ቶፕ ኮምፒውተር ይከፈታል ወግ ይጠረቃል ፤ፖለቲካ ይታሻል ፤ይወቀጣል፤ ትንታኔ ይሰጥበታል፤ ዓለም እንዴት ሰነበተች እንላለን ማነው ቴሌቪዥን መስኮት ላይ ብቻ ለሚቀርቡት  ጋዜጠኞች የፈቀደው ???

Wednesday, April 25, 2012

አዳም ወ apple


        አንዳንድ ጊዜ ይገርመኛል ይህቺን ግጥም ስጽፍ አንድም መረዝ መደለዝ አላጋጠመኝም በቃ እንደወረደ ነው ያስቀመጥኩት ፡፡ አንዲህ የሚሆነው አንድም ነገሩ በደንብ ስሜቱ ነክቶሃል ! ወይም ቅርብ አደር ትሆናለህ…….!፡፡ ልደቴ  ቀን ነው የተጻፈው ያስቃችሁ፤ወይ ያስገርማችሁ፤ወይ ያናድዳችሁ እንደሁ የምትሉትን እቀበላለሁ፡፡