Wednesday, May 2, 2012

ልዑል ዓለማየሁ


                              ልዑል ዓለማየሁ

        ዓፄ ቴዎድሮስ ደራስጌ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተቀምጠው ሳለ አንድ ወታደራቸው ወደ ርሳቸው ቀረበና "ጌታዬ አንዲት ሴት አገኘሁ ፊትዋም እንደ ፀሐይ የሚያበራ ነው" አላቸው:: ልጅቱም በኃላ ወደ ቤተ መንግስት ቀረበች: ስምዋም ጥሩነሽ ውቤ የደጃዝማች ውቤ ኃይለማርያም ልጅ ነበረች::
ንጉሱም አይተዋት "እውነትም ወርቅ ናት" በማለት አገብዋት::
በዚህ ወቅት ንጉሠ ነገሥቱ አባትዋን ራስ ውቤን አስረዋቸው ነበር:: ራስ ውቤ የሰሜን ወልቃይት; ፀገዴ; ትግራይ; ሰራየ; ሐማሴንና; አንጎት(ሰሜን ወሎ) አስተዳዳሪ ሲሆኑ:: ከአፄ ፋሲለ ደስ የሚወለዱ ስለነበሩ: ለንጉሥነት የሚገዳደሩ ነበሩ::
የጥሩወርቅ(ጥሩነሽ) እናት ደግሞ ወይዘሮ ላቂያየ የተባሉ: የትግራይ መሣፍንት ዘር ነበሩ::
ከኒህ ሚስታቸው ደጃዝማች ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የተባለውን: ከሁሉ በላይ የሚወዱትን እርሳቸውን እንዲተካ ያጩትን ልጅ ወለዱ::

ልዑል ዓለማየሁ 1853/ ተወልደው: በምርኮ በተወሰዱበት እንግሊዝ አገር ሊድስ ዩርክሻየር 1870/ ሃገሬ ናፈቀችኝ እንዳሉ 17ዓመት ዕድሜያችው በሣንባ ምች ታመው ዓረፉ::

1 comment: