Monday, May 21, 2012

ጥላ….ሁን ለነፍሴ


ዘመን ዘመነና ከግዜ ደጃፍ ላይ
ትዝታን ቀስቅሶ አይኔ እውነቱን ሊያይ
ለእድሜ እድሜ ይስጠው ለዚህ ቀን ካበቃኝ
እፎ…ይ ልበል በቃ ቋጥሬልህ ስንኝ፡፡
ነፍሴ ጮቤ ረገጠች
ሲቃ ተናነቃት ልቤም ተባረከች
ላለፉት ጣፋጭ ግዜያቶች
ለመድረክ ላይ ገድልህ
አንተን ልታስብህ ቃልት አጣችለት
ደፍሬ ልድፈርህ ነፍሴ ደስ ይበላት፡፡
‘ዋይ…ዋይ ሲሉ የርሀብን ጉንፋን ሲስሉ’
አብረህ ብታለቅስ ቢመጣብህ ምስሉ
‘እሩቅ ምስራቅ’ ሄደህ በመንፈስ አፍቅረህ
በየጦር ግንባሩ በወኔ ታጅበህ
‘ገንዘብ አውጡ ስሩ’
‘ቀጠሮም አክብሩ’
ብለህ አስተምረህ
ካዘነው ስታዝን ከሳቀውም ስቀህ
በዜማ ጽላጼ ለኛነት ታድመህ
እልፍ ሳትነጥፍ አግተህ
ጥ…ላሁን አለችህ እናትህ
ሀሴት ስንሞላ ታይቷት ጥላነትህ፡፡
የልጅነት ግዜን ያፍላነት ቡረቃን
የጣፋጭ ትዝታን የማይጠገብን
በተቀደሰው በሞቀው ፍቅራችን
እጃችን ተቋልፎ አንገት ላንገት ታንቀን
እንባ ግድቡን ጥሶ
ጉንጫችን ረስርሶ
“የህይወቴን ህይወት” እኩል ዘመርንበት
ትፍስትን ለግሶ ሊያገባን ከገነት፡፡
አወይ የመሰጠት መታደል ብዛቱ
እንደ ፏፏቴ ሲፈስ ቃላት ካንደበቱ
በርቦ ተቆንጥሮ ላያልቅ ደግነቱ
ግማሽ ዘመን ሙሉ
እመድረክ ላይ ነግሰህ
ደንሰህ አልቅሰህ
እኛን መስለህ እኛን ኖረህ
ውስጣችን አንኳኩተህ
እርግጥ ነው……
ሰው መቼም ሞትን ይሞታል
ያለነው በፊትም
ሞትን ግን ማሸነፍ
በስራ ተግባሩ
አንተ ድል አድርገህ
                 ዘመን ሲሻገሩ
አየሁት በግርምት እስከሙሉ ክብሩ
እድሜ ጠግቦ ዛሬ በዳግም ትንሳኤ
                ሞትና ልደቱ፡፡
አሀዱ እንዳልክባት እንደ“ጥላ ከለላ”
           ሺ ዘመን ትኖራለህ
ቅርጽ ነህ ላገርህ ሙሽራ ሁን ለኛ፡፡
*   *   *
አደም ሁሴን
 4/3/2003ዓም

No comments:

Post a Comment