Wednesday, October 10, 2012

ጥቁሩ ክረምቴ


ጎበዝ ሃብታምና ደሃ በሃገሬ እና በመላው ዓለም ልዩነቱ እየሰፋ መሆኑ እየተሰማኝ ነው ወይም የኔ ስሌት ይህን ያመለክታል ፡፡ እዚህ ጋር ቀናነት የህሊና ዳኝነት ትልቁን ሚና ይጫወታል ፍርሃዊ የሃብት ክፍፍል……! ሲባል ቃሉ ቀላል ሊመስል ይችላል ነገሩ ግን ከዛም በላይ ነው፡፡ ለምን ?እንዴት ?ለሚለው ግን በጉዳዩ ላይ ያሉ ሰዎች መልስ የሚሰጡት ነው የሚሆነው፡፡
ወደ ዛሬው ጉዳይ እንምጣ ከዛሬ 13 ዓመት በፊት በአንድ አጋጣሚ በመዲናችን በበጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማሩ እትዮÉያዊት አግኝቼ ብዙ አወራን እጅግ ልብ የሚነካ ጨዋታ ተጫወትን…… ቤትና ወላጅ አልባ ሕጻናትን፤ጧዋሪ አልባ አረጋዊያንን ነው የሚንከባከቡት…….፡፡.
ለዚህ
ቀና ተግባር እንዴት ሊነሳሱ እንደቻሉ፤በቀጣይ ምን ሊሰሩ እንዳሰቡ እንዲሁም በዚሁ ሂደት ላይ ሰዋዊ እና ተፈጥሮዋዊ መሰናክሎች እንዴት እንደገጠሟቸው እና ይሄን መሰናክል እንዴት እንዳለፉት በሰፊው አጫወቱኝ፡፡ የበጎ አድራጎት ስራ ሀገሬ ላይ ብዙ እንዳልተለመደና ትኩረት ቢሰጠው ሰው ያለውን እውቀቱን፤ንብረቱን፤ጉልበቱን ለሌለው ፤ለተቸገረ ማካፈልን ቢለምድ ከጥንት የወረስነውን መረዳዳትና መደጋገፍን ባህሉ አድርጎ ቢቀጥል ቢያንስ ሰው ሃገሩን ጥሎ እንደማይወጣ የራበው ጠግቦ እንደሚያድር አጫወቱኝ….፡፡ አቦ ከዚ በላይ ማለት አልችልም ሌላ ቀን ሉላ ቀን እናውራ በዚህ ጉዳይ ሰፊ ጽሁፍ አቀርባለሁ ብዪ ልገምት ለዛሬ በዚሁ ጉዳይ ልቤን ነክቶት የጫርኳት በዚህች ግጥም ተዝናኑ ተወያዩ የዛ ቀን ይበለን ሌላም እንጽለን…….!

No comments:

Post a Comment