Wednesday, October 10, 2012

መጽሐፍ የሚያነብ ትውልድ እንፍጠር !!!


ትንሳኤው ናፈቀኝ


በርካታ የአለማችን ህዝቦች እንደመብላትና መጠጣት ከዛም በላይ የመናገር የመጻፍ እና ሃሳብ የመስጠት መብታቸው ተገፎ በመሸማመቅ ባለመኖር መኖር የእንጥልጥል ህይወት የሚመሩ ቤት ይቁጠራቸው…..! ፡፡ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ሰፋ አድርጌ አስባለሁ ፤ሳላውቀው እጨነቃለሁ፤ ለምን ግን እላለሁ…..! ይሄ የአንድ ጤነኛ ሰው አስተሳሰብ ነው ብዩ ባስብም ከዛ በላይ ምን አደርጋለሁ ? ይህ ጉዳይ ስሜቴን ሲነካኝ በግጥም አስፍሬ አስቀመጥኳት፡፡ እስቲ እዮብ፤ዘላለም ጥላሁን፤ዮናስ እንዲሁም ሌሎች ወዳጆቼ በቀና መንፈስ ተወያዩ….. መልካም ንባብ፡፡

ስራ ክቡር ነው..!!


ይድነቃቸው በቃ…!!!


ጥቁሩ ክረምቴ


ጎበዝ ሃብታምና ደሃ በሃገሬ እና በመላው ዓለም ልዩነቱ እየሰፋ መሆኑ እየተሰማኝ ነው ወይም የኔ ስሌት ይህን ያመለክታል ፡፡ እዚህ ጋር ቀናነት የህሊና ዳኝነት ትልቁን ሚና ይጫወታል ፍርሃዊ የሃብት ክፍፍል……! ሲባል ቃሉ ቀላል ሊመስል ይችላል ነገሩ ግን ከዛም በላይ ነው፡፡ ለምን ?እንዴት ?ለሚለው ግን በጉዳዩ ላይ ያሉ ሰዎች መልስ የሚሰጡት ነው የሚሆነው፡፡
ወደ ዛሬው ጉዳይ እንምጣ ከዛሬ 13 ዓመት በፊት በአንድ አጋጣሚ በመዲናችን በበጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማሩ እትዮÉያዊት አግኝቼ ብዙ አወራን እጅግ ልብ የሚነካ ጨዋታ ተጫወትን…… ቤትና ወላጅ አልባ ሕጻናትን፤ጧዋሪ አልባ አረጋዊያንን ነው የሚንከባከቡት…….፡፡.
ለዚህ
ቀና ተግባር እንዴት ሊነሳሱ እንደቻሉ፤በቀጣይ ምን ሊሰሩ እንዳሰቡ እንዲሁም በዚሁ ሂደት ላይ ሰዋዊ እና ተፈጥሮዋዊ መሰናክሎች እንዴት እንደገጠሟቸው እና ይሄን መሰናክል እንዴት እንዳለፉት በሰፊው አጫወቱኝ፡፡ የበጎ አድራጎት ስራ ሀገሬ ላይ ብዙ እንዳልተለመደና ትኩረት ቢሰጠው ሰው ያለውን እውቀቱን፤ንብረቱን፤ጉልበቱን ለሌለው ፤ለተቸገረ ማካፈልን ቢለምድ ከጥንት የወረስነውን መረዳዳትና መደጋገፍን ባህሉ አድርጎ ቢቀጥል ቢያንስ ሰው ሃገሩን ጥሎ እንደማይወጣ የራበው ጠግቦ እንደሚያድር አጫወቱኝ….፡፡ አቦ ከዚ በላይ ማለት አልችልም ሌላ ቀን ሉላ ቀን እናውራ በዚህ ጉዳይ ሰፊ ጽሁፍ አቀርባለሁ ብዪ ልገምት ለዛሬ በዚሁ ጉዳይ ልቤን ነክቶት የጫርኳት በዚህች ግጥም ተዝናኑ ተወያዩ የዛ ቀን ይበለን ሌላም እንጽለን…….!

አንድ ቃል ነበረ…!!!


ህያው አንድነቶች…!!!


ይህችን ግጥም እጅግ በጣም ለማደንቀው ድምጻዊ ገጣሚና የዜማ ደራሲ ለሆነው ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ለአዲስ ትዳሩ እንዲሁም በፍቅር አለም ጥንድ ሆነው ለሚኖሩ፤ ተጋብተው…ቤተሰብ ለመሰረቱ ትሆን ዘንድ ፈቀድኩ ከተመቻችሁ ሼር በማድረግ ተገባበዙ መልካም የፍቅር አመት ያድርግልን፡፡